በ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የአማራ ተፈናቃዮች የአማራ ብልፅግና አገዛዝ ግድያ ሊያስፈፅምብን ነው አሉ፡፡

 ethiopian human right commussion
October 2023

by voice of fano

የአማራ ህዝብ በኦነግ ሸኔ ብልፅግና እና በብአዴን የሚደርስበት መሳደድ እና ግፍ እሰከ መጠለያ ጣቢያ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ከመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የአማራ ተፈናቃዮች የአማራ ብልፅግና አገዛዝ ግድያ ሊያስፈፅምብን ነው ብለዋል፡፡ በኦሮሚያ ክልል የአብይ ገዳይ ቡድን፣በኦሮሚያ ልዩ ኃይልና በሽብርተኛው አኦነግ ሸኔ ተፈናቅለውና ተዘርፈው በደብረብርሃን መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች ያለ ምንም ዋስትና ወደ መጣችሁበት ተመለሱ መባላችን ለከባድ ስጋት አጋልጦናል ብለዋል፡፡

እኛ አማራ በመሆናችን ብቻ ፣ “ወገኖቻችን ቀብረን ፣ ንብረታችን ተዘርፈን፣ አካላቸው የጎደለ ወገኖቻችን እና ሕይወታችንን ብቻ ይዘን ከገዳዮቻችን በተዐምር አምልጠን የወጣን ሰዎች ነን ያሉ ሲሆን ። አማራ ጠል የሆኑት የአገዛዙ ከድሬዎች ሰጡት በተባለ ምላሽ ደግሞ፤ የተዘረፈባችሁን ንብረት ከዚያው ከቦታችሁ ስትሄዱ እናስመልስላችዋለን፤ የተዘረፋችሁትን ንብረትና ቤተሰቦቻችሁን አስመዝግቡ ማለታቸው ተሰምቷል፡፡

የሞቱ ወገኖቻችን እስካሁን ፍትሕ ባላገኙበትና ሽብርተኛው ቡድን አሁንም እየዘረፈ እና እየገደለ ባለበት ሁኔታ እናንተን በምን እናምናችዋለን? ምንስ አቅም አላችሁ? የሚል ጥያቄ ከተፈናቃዮች በኩል ተደጋግሞ መነሳቱን የመረጃ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ተፈናቃዮቹ አክለውም፣ መንግሥት ለምን አልሞታችሁም በሚል መልኩ ድጋሚ ለገዳይ ኃይሎች አሳልፎ ሊሰጠን እንደሆነ በተደጋጋሚ መረጃዎች ደርሰውናል ብለዋል፡፡ "ከሽብርተኛው ሸኔ በባሰ መልኩ እኛን ለጥቃት ያጋለጠን የኦሮሚያ መንግሥት ነው።" የሚሉት ተፈናቃዮቹ፣ የአማራ ብልፅግና አመራሮች ለርካሽ የፖለቲካ ትርፍ ግድያ ሊያስፈፅሙብን ይችላሉ በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል፡፡ በሽብርተኛ ቡድን ሰበብ ለዓመታት ከኖሩበት ቀያቸው ተፈናቅለው በደብረብርሃን መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ የአማራ ተወላጆች አሁንም አስከፊ ሕይዎትን እያስተናገዱ መሆናቸውን በምሬት ተናግረዋል፡፡ ለዚህ በደል እና እንግልት መፈናቀል እና መሳደድየ የአማራ ፋኖ እየታገለ ያለዉ ድል ለአማራ ፋኖ! ድል ለአማራ ህዝብ! Voice of fano መረጃ